Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ 5 ጨዋታዎች ይደረጋሉ

Erling Haaland of Manchester City celebrates his goal to make it 4-1 during the Premier League match between Manchester City and Burnley at the Etihad Stadium, Manchester, England. Saturday 27th September 2025. (Photo by Lexi Isley / Manchester City)

አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ7ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ አምስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በዚህ መሰረትም ቀን 10 ሰዓት ላይ አስቶንቪላ ከበርንሌይ፣ ኤቨርተን ከክሪስታል ፓላስ፣ ኒውካስል ዩናይትድ ከኖቲንግሃም ፎረስት እንዲሁም ዎልቭስ ከብራይተን ይጫወታሉ፡፡

በተጨማሪም ምሽት 12፡30 ማንቼስተር ሲቲ ወደ ለንደን አቅንቶ ብሬንትፎርድን በቴክ ኮሚኒቲ ስቴዲየም የሚገጥም ይሆናል፡፡

ባለፉት ጨዋዎች 10 ነጥብ በመሰብሰብ በሊጉ 8ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡት ሲቲዝኖቹ ÷ የዛሬውን ጨዋታ ካሸነፉ ደረጃቸውን ወደ 5 ከፍ ማድረግ ይችላሉ፡፡

Exit mobile version