አዲስ አበባ፣ መስከረም 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በደሴ ከተማ የሚገኘውን የሆጤ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የማስፋፊያ ግንባታ መርቀዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር መልሶ ማቋቋም መርሐ ግብር የተከናወነው የማስፋፊያ ግንባታው 12 ክፍሎች እንዳሉት ተመላክቷል፡፡
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር)፣ የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ ሳሙኤል ሞላልኝ እና ሌሎች የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
በእሸቱ ወ/ሚካኤል
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!