Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የምድብ 9ኛ ጨዋታውን ያደርጋል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ 9ኛ ጨዋታውን በዛሬው ዕለት ከጊኒ ቢሳው ጋር ያደርጋል፡፡

ከ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ መሆኑን አስቀድሞ ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን መርሐ ግብር ለማሟላት ነው ጨዋታውን የሚያካሂደው፡፡

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በማጣሪያው ካደረጋቸው 8 ጨዋታዎች አንዱን ብቻ ሲያሸንፍ ÷ በሶስቱ አቻ እንዲሁም በአራቱ ደግሞ ተሸንፏል፤በዚህም በ6 ነጥብ 5ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

በሌላ በኩል የዋልያዎቹ ተጋጣሚ ጊኒ ቢሳው ካደረጋቸው 8 ጨዋታዎች 10 ነጥብ በመሰብሰብ በምድቡ 4ኛ ደረጃ ተቀምጧል፡፡

የሁለቱ ብሄራዊ ቡድኖች ጨዋታ ቀን 10 ሰዓት ላይ በሩዋንዳ ኪጋሊ አማሆሮ ስታዲየም የሚካሄድ ይሆናል፡፡

ምድቡን ግብጽ በ20 ነጥብ ስትመራ ቡርኪነፋሶ በ15፣ ሴራሊዮን በ12፣ ጊኒ ቢሳው በ10፣ ኢትዮጵያ በ6 እንዲሁም ጂቡቲ በ1 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 6ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version