Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት በልዩ ትኩረት ይሰራል- አቶ ኦርዲን በድሪ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በአገልግሎት አሰጣጥና ዙሪያ ከወረዳ አስተዳዳሪዎች ጋር ተወያይተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት÷የአገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል ረገድ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በወረዳዎች የማሕበረሰቡን የአገልግሎት አሰጣጥ ሁኔታ በማሻሻል ፍትሃዊ፣ ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል፡፡

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከልና በማረም መልካም አስተዳደር ከማስፈን እንዲሁም የልማት ሥራን ከማፋጠን ጎን ለጎን ለጸጥታ ጥበቃ ሥራ ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።

ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ በክልሉ በኮሪደር ልማት የተመዘገበውን ውጤት ለማስፋት ይሰራል ነው ያሉት፡፡

የኮሪደር ልማት ሥራውን በውስጥ ለውስጥ መንገዶች በማስፋት ከዋና መንገዶች ጋር ለማገናኘት እንደሚሰራ መናገራቸውንም የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሄኖክ ሙሉነህ ለፋና ዲጂታል ገልጸዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version