Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

15ኛው የኢትዮጵያ ኢቫሉዌሽን አሶሴሽን ዓመታዊ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 15ኛው የኢትዮጵያ ኢቫሉዌሽን አሶሴሽን ዓመታዊ ጉባኤ “ሀገራዊ የእቅድና ምዘናን አቅም ማሳደግ” በሚል መሪ ሐሳብ እየተካሄደ ይገኛል።
ጉባኤውን የኢትዮጵያ ኢቫሉዌሽን አሶሴሽን ከፕላንና ልማት ሚኒስቴር፣ ጅማ ዩኒቨርሲቲ እና ዩኒሴፍ ጋር በትብብር ያዘጋጁት ሲሆን÷ ከተለያዩ የመንግሥት ተቋማትና ከአራት ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ከ150 በላይ ተሳታፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በጅማ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ በሚገኘው መድረክ በሚኒስቴሩ የተዘጋጀ የእቅድ፣ ክትትል እና ግምገማ ምዘና ፖሊሲ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ጥሩማር አባተ ሚኒስቴሩ የክትትልና ግምገማ ስርዓትን ለመገንባት እና ዲጂታላይዝ ለማድረግ፣ ጥራት ያለውን መረጃ ለማመንጨት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) በበኩላቸው÷ ማንኛውም የልማት ግብና ሀገራዊ ግንባታ የሚጀመረው ከእቅድ መሆኑን አንስተው÷ ዩኒቨርሲቲውም የሰው ኃይልን በማሰልጠን የተለያዩ ምርምሮችን በማካሄድ ከእቅድና ግምገማ ከተቋማት ጋር እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኢቫሉዌሽን አሶሴሽን ፕሬዚዳንት ደረጀ ማሞ ማሕበሩ በመንግሥት ተቋማት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት በአቅም ግንባታ ላይ እየሰራ መሆኑን አመላክተዋል።
በበሪሳ ኃ/ማርያም
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!
Exit mobile version