አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ50ኛው በኔዘርላንድስ አምስተርዳም ማራቶን የሴቶች ውድድር አትሌት አይናለም ደስታ አሸንፋለች፡፡
በውድድሩ ብርቱካን ወልዴ 2ኛ ስትወጣ መቅደስ ሽመልስ 3ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ላለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት የአምስተርዳም ማራቶንን ማሸነፍ ችለዋል፡፡
የአምስተርዳም ማራቶን በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ ያለው ነው።