Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባዔ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ካቶሊክ ጳጳሳት ጉባዔ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማውን ሐዘን ገልጿል፡፡

ጉባዔው ባስተላለፈው የሐዘን መግለጫ መልዕክት ÷ የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን በታላቁ አባት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማትን ጥልቅ ሐዘን ትገልጻለች ብሏል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ የብዙዎች አባት፣ የሰላም እና የአንድነት ተምሳሌት ነበሩ፤ ሀገራችን ታላቅ አባትን አጥታለች ሲል ገልጿል፡፡

ከኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጋር በተለይም በሀገራችን ሰላም እና እርቅን ለማውረድ በርካታ ሥራዎችን በጋራ እንደሰሩም አውስቷል፡፡

ጉባዔው ለቤተቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለእስልምና እምነት ተከታዮች እና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ መጽናናትን ተመኝቷል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version