Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አርባ ምንጭ ከተማ እና ባህር ዳር ከተማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሁለተኛ ሳምንት የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባ ምንጭ ከተማ ባህር ዳር ከተማ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡

አርባ ምንጭ ከተማ ታምራት ኢያሱ በ76ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠራት ግብ ሲመራ ቢቆይም በጨዋታው መገባደጃ ግርማ ዲሳሳ ባህር ዳር ከተማን አቻ ማድረግ ችሏል፡፡

በአሁኑ ሰዓት መቐለ 70 እንደርታ ከመቻል በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

ሊጉ ሲቀጥል ቀን 10 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በአዲስ አበባ ስታዲየም እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከምድረ ገነት ሽረ ጋር ይጫወታሉ፡፡

Exit mobile version