Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በአዋሽ ፈንታሌ ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ የተሰማ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ዛሬ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል አለ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ ሕዋ ሳይንስና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት።

በዩኒቨርሲቲው የሶሲሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ አታላይ አየለ (ፕ/ር)፥ በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 8 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ለፋና ዲጂታል አረጋግጠዋል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ከጠዋቱ 2 ሰዓት ከ24 ደቂቃ አካባቢ መከሰቱን ገልጸዋል።

የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረትም አዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ የተለያዩ አካባቢዎች ድረስ መሰማቱን ነው የገለጹት።

በአድማሱ አራጋው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version