Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ዛሬ አርሰናል ከክሪስታል ፓላስ እና አስቶን ቪላ ከማንቼስተር ሲቲ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዛሬ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ከክሪስታል ፓላስ እንዲሁም አስቶን ቪላ ከማንቼስተር ሲቲ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።

በ9ኛው ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አምስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።

በዚህም አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የሊጉ መሪ አርሰናል ክሪስታል ፓላስን የሚገጥምበት ጨዋታ ይጠበቃል።

በውድድር ዓመቱ አርሰናልን የተቀላቀለው ኤበሪቼ ኤዜ የቀድሞ ቡድኑን በሚገጥምበት በዚህ ጨዋታ መድፈኞቹ የሉጉን መሪነት ለማስቀጠል ሲገቡ÷ በተለይም ካለፈው ዓመት ጀምሮ ድንቅ ብቃት እያሳየ ከሚገኘው ክሪስታል ፓላስ ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል።

በተመሳሳይ ሰዓት አስቶን ቪላ ከማንቼስተር ሲቲ ጨዋታቸውን የሚያደርግ ሲሆን÷ ከአርሰናል በ3 ነጥብ ዝቅ ብሎ 3ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ሲቲ ጨዋታውን በማሸነፍ የነጥብ ልዩነቱን ለማጥበብ ወደ ሜዳ ይገባል።

በተጨማሪም ወልቭስ ከበርንሌይ እና በርንማውዝ ከኖቲንግሃም ፎረስት ጋር ጨዋታቸውን በተመሳሳይ ሰዓት ሲያደርጉ÷ ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ኤቨርተን ከቶተንሀም ጋር ይጫወታል።

ትናንት በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎቸ ቼልሲ እና ሊቨርፑል በተጋጣሚዎቻቸው ሲሸነፉ ማንቼስተር ዩናይትድ ማሸነፋ ይታወሳል።

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version