Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ በውሃ ሃብት ጥበቃ ላይ ትርጉም ያላቸውን ስራዎች እየሰራች ነው – ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የውሃ ሃብት ጥበቃና አጠቃቀምን በተመለከተ ትርጉም ያላቸውን ስራዎች እየሰራች ነው አሉ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)።

ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት በ2ኛው የውሃ እና ኢነርጂ ሳምንት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ ነው።

ኢትዮጵያ የውሃ ሃብት ጥበቃ ላይ የምትሰራው ስራና የኃይል ልማት ተግባራት ለሌሎች ትምህርት ሊሰጥ የሚችል እንደሆነም ሃብታሙ (ዶ/ር) ተናግረዋል።

ለአምስት ቀናት በአዲስ አበባ በሚካሄደው የውሃ እና ኢነርጂ ሳምንት ዐውደ ርዕይና ፓናል ውይይቶች እንደሚደረጉ ተገልጿል።

በፓናል ውይይቱ የውሃ ሃብት አጠቃቃም እና አስተዳደር የተመለከተ እንዲሁም ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች አጠቃቀም ላይ ያሉ ልምዶችን የተመለከቱ ጉዳዮች ይዳሰሳሉ።

በለይኩን ዓለም

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version