Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ነዳጅ የመቀሸብ የወንጀል ድርጊት በመፈጸም የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፋር ክልል ነዳጅ የመቀሸብ የወንጀል ድርጊት በመፈጸም የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጸው፤ በሰመራ ሎጊያ ከተማ ከጅቡቲ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የነዳጅ ምርቶች ላይ ቅሸባ እንደሚፈጸምበት በተጠረጠረ ስፍራ ክትትል ተደርጓል።

በዚህም ክትትል ተደርጎ በተሰባሰበው መረጃ መሰረት ከአንድ የነዳጅ ጫኝ ተሸከርካሪ ቦቴ ነዳጅ በመቀነስ ሲሸጡና ሲገዙ የተገኙ 10 ተጠርጣሪ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ነው።

በአካባቢው በሳጠራ ከተሰሩ 13 ቤቶች ውስጥ በነዳጅ የተሞሉ በርሜሎች እንደተከማቹ መገለጹን ያመለከተው መረጃው፤ እስካሁን በተደረገ ብርበራ 49 በርሜል ናፍጣ መያዙን ገልጿል።

ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ወሳኝ የሆነውን የነዳጅ ምርት ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በመቀሸብ ለብክነት እና ለአደጋ በሚያጋልጥ ሁኔታ የአቅርቦትና ስርጭት ስራን ማስተጓጎል በነዳጅ ግብይት አዋጅ መሰረት ያስጠይቃል።

በሀገር ላይ የሚፈፀሙ የኢኮኖሚ አሻጥሮችን በመከላከል ጥፋተኞችን ተጠያቂ በማድረግ የነዳጅ ግብይቱን ሕጋዊ መስመር ለማስያዝ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብሏል።

በመሳፍንት እያዩ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version