Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ ሩዋንዳን 2 ለ 0 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሴካፋ ከ17 ዓመት በታች የማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያ ሩዋንዳን 2 ለ 0 አሸንፋለች።

በዛሬው ዕለት በተጀመረው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ (ሴካፋ) ከ17 ዓመት በታች የማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያን አሸናፊ ያደረጉትን ሁለት ግቦችን ዳዊት ካሳ እና ሁዘይፋ ሻፊ አስቆጥረዋል።

በተመሳሳይ ውድድር ቀን 7፡00 ላይ በተካሄደው የመክፈቻ ጨዋታ ሶማሊያ እና ደቡብ ሱዳን 2 ለ 2 በሆነ የአቻ ውጤት ተለያይተዋል።

እንዲሁም መርሐ ግብሩ ቀጥሎ ሲካሄድ ምሽት 11:00 ሰዓት ላይ ታንዛኒያ ከ ሱዳን እንዲሁም ምሽት 2:00 ቡሩንዲ ከ ዩጋንዳ ይጫወታሉ።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version