Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኮሪደር ልማት ቅርሶችን ጠብቆ ማቆየት አስችሏል – አቶ ኦርዲን በድሪ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በክልሉ የተከናወነው የኮሪደር ልማት ቅርሶችን ጠብቆ ማቆየት አስችሏል አሉ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ የኮሪደር ልማት ስራዎች በተመዘገበው ውጤት አሻራቸውን ላኖሩ ተቋማት እና ማህበራት የእውቅና ሽልማት አበርክተዋል።

ዓለም አቀፉ የጁገል ቅርስ ተንከባካቢ በማጣት በዩኔስኮ የተሰጠውን እውቅና የመነጠቅ አደጋ ውስጥ ገብቶ እንደነበር አቶ ኦርዲን በዚህ ወቅት አስታውሰዋል።

በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመነጪነት የተመጀረው የኮሪደር ልማት በቅርሱ ላይ የተጋረጠውን አደጋ መቀልበስ ብቻ ሳይሆን ክልሉን በሀገር አቀፍ ደረጃ ተምሳሌት ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማት ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል በመፍጠር ዓለም አቀፉን የጁገል ቅርስ የመላው ኢትዮጵያና የዓለም ሀብት መሆኑን ግንዛቤ ማስረፅ መቻሉን ጠቅሰዋል።

በክልሉ በኮሪደር ልማት የተገኘው ውጤት ለቀጣይ ስራ የሚያነሳሳ መሆኑንና የተጀመሩትን የልማት ስራዎችን ፍጥነት በመጨመር በማጠናቀቅ በቀጣይ ጅምር ስኬቶችን ለማስፋት ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ማለታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ ለፋና ዲጂታል ገልጸዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version