Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በበጀት ዓመቱ 250 ሚሊየን ቶን መኖ ለማምረት እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በተያዘው በጀት ዓመቱ 250 ሚሊየን ቶን መኖ ለማምረት እየተሰራ ነው አለ የግብርና ሚኒስቴር።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት÷ በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 91 ሚሊየን ቶን መኖ ማምረት ተችሏል።

ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ፣ ቢሾፍቱ፣ አዳማ እና ባሕር ዳር ብቻ የነበሩት የመኖ ማቀነባበሪያዎች አሁን ላይ በሁሉም ክልል የዞን ከተሞች እንዲስፋፉ ተደርጓል ብለዋል።

በቅርቡም 15 የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽነሪዎች ለክልሎች መሰራጨታቸውን ተናግረዋል።

መኖ በየቦታው እንዲመረት እና ማቀነባበሪያዎችም እንዲስፋፉ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸው÷ በየጊዜው የመኖ ዋጋ ላይ ሲነሳ የነበረውን 15 በመቶ ተጨማሪ እሴት ታክስ ለማስነሳት ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል።

በዙፋን ካሳሁን

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version