Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

12ኛው ሀገር አቀፍ የጥራት ሽልማት በመጪው ቅዳሜ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 12ኛው ሀገር አቀፍ የጥራት ሽልማት መርሐ ግብር በመጪው ቅዳሜ ይካሄዳል፡፡

የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት በየዓመቱ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችን በዓለም አቀፍ የጥራት ሥራ አመራር መለኪያ መስፈርት በማወዳደር ዕውቅና እና ሽልማት ይሰጣል።

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ መብራት የዘንድሮውን ሀገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ሥነ ሥርዓት አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት÷ በውድድሩ ከተመዘገቡት 65 ድርጅቶች ውስጥ 63 ድርጅቶችና ተቋማት እስከ መጨረሻ ደርሰዋል፡፡

ከተመዘገቡ ተቋማትና ድርጅቶች 34 በአምራች ዘርፍ፣ 12 ለትርፍ የተቋቋሙ አገልግሎት ሰጪዎች፣ 10 በጤና ዘርፍ፣ 5 በአገልግሎት ዘርፍ፣ 3 በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ እና 1 በኮንስትራክሽን ዘርፍ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

የሽልማት ሥነ ሥርዓቱ በታላቁ ቤተ መንግሥት እንደሚካሄድ ጠቅሰው÷ ውድድሩ 7 የአሰራር ሥርዓት መስፈርቶች እንዳሉት ተናግረዋል።

በ2000 ዓ.ም የተቋቋመው የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ለጥራት ልዩ ትኩረት የሚሰጥ የሽልማት ሥርዓት በመዘርጋት የሀገሪቱን ዓለም አቀፍ የተወዳዳሪነት ብቃት በማሳደግ ጥራት የሀገሪቱ ባህል እንዲሆን ማድረግን ያለመ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

በሽልማት ሥነ ሥርዓቱ ላይ የድርጅቱ የበላይ ጠባቂ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡

በአንዷለም ተስፋዬ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook WMCC
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version