Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በማያቋርጥ መፍጠር እና መፍጠን መርህ እየሰራን የኢትዮጵያን ብልፅግና እናረጋግጣለን – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በማያቋርጥ መፍጠር እና መፍጠን መርህ እየሰራን የኢትዮጵያን ብልፅግና እናረጋግጣለን አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።

በአዲስ አበባ ከተማ ‘በመደመር መንግሥት እይታ የዘርፎች እመርታ’ በሚል መሪ ሐሳብ ለብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ባለፉት ቀናት ሲሰጥ የነበረው 2ኛ ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቅቋል።

ከንቲባዋ በማጠቃለያው ላይ እንዳሉት፤ አመራሩ በሁሉም መስኮች በስልጠናው ያገኘው ግንዛቤ በተጨባጭ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት እና የተገኙ አበረታች ውጤቶችን የመስክ ምልከታም አካሂዷል።

በሁሉም መስኮች የተመዘገቡ ስኬቶችን በማስቀጠልና ተግዳሮቶችን ወደ ድል በመቀየር፣ የተሻለችና የብልፅግና ተምሳሌት የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ትኩረት እንዲደረግባቸው አስገንዝበዋል።

በለየናቸው የትኩረት ዘርፎች የግብርና እና ገጠር ትራንስፎርሜሽን፣ የኢንዱስትሪ እንዲሁም የቱሪዝምና ከተማ ልማት ዘርፎች እመርታን ለማስመዝገብ መግባባት ፈጥረናልም ነው ያሉት።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook WMCC
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version