Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓልን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት ተጠናቋል

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 20ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በድምቀት ለማክበር አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል አለ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ።

የዘንድሮው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሀሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡

የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ ተመስገን ካሳ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፥ በዓሉ ያለምንም የጸጥታ ችግር በድምቀት ተከብሮ እንዲጠናቀቅ የፀጥታ ኮሚቴ ተዋቅሮ ከአጎራባች ክልሎች ጋር በመተባበር የቅድመ ዝግጅት ስራ ተሰርቷል፡፡

ዕለቱ ክልሉን ይበልጥ ለማስተዋወቅ የሚያስችል መሆኑን ገልጸው፥ እንግዶች ወደ በዓሉ መጥተው እስከሚመለሱ ድረስ ደህንነታቸው የተጠበቀ እንዲሆን ዝግጅት ተደርጓል ነው ያሉት።

በሰለሞን በየነ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version