Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ከሕዝብ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ መንግሥት በቁርጠኛነት ይሰራል – ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከሕዝብ የሚነሱ ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ እንዲያገኙ ለማስቻል መንግሥት በቁርጠኛነት ይሰራል አሉ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ።

“የጉባ ብስራቶች ፤ የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች” በሚል መሪ ሃሳብ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ እና የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ በተገኙበት በሆሳዕና ከተማ ሕዝባዊ ውይይት ተካሂዷል።

ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልሉ እየመጣ ያለው ለውጥ የክልሉ መንግሥት እና ማህበረሰቡ ተደማምጠው እየሰሩ ስለመሆናቸው ማሳያ ነው።

ከክልሉ ሕዝቡ የሚነሱ ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ እንዲያገኙ ለማስቻል መንግሥት በቁርጠኛነት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል።

እናትዓለም መለሰ በበኩላቸው፤ ማህበረሰቡ የነበረውን ትብብር በማጠናከር በሚያጋጥመው ችግር ላይ በጋራ በመሥራት የመፍትሔ አካል ሊሆን ይገባል ብለዋል።

ከዚህ በፊት በተከታታይ በተደረጉ ውይይቶች የተነሱ ጥያቄዎች እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች እየተቀረፉ እንደሚገኙ የገለጹት ደግሞ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማና ኢንዱስትሪ ልማት ክላስተር አስተባባሪ ስንታየሁ ወ/ሚካኤል ናቸው።

በውይይት መድረኩ የተነሱ ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እና በፍጥነት ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

በውይይቱ የተሳተፋ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች መንግሥት እየሰራቸው የሚገኙ ሁሉን አቀፍ የልማት ሥራዎች የክልሉን ማህበረሰብ እኩል ተጠቃሚነት ያረጋገጠ መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይም የንፁህ መጠጥ ውሃና መብራት፣ የመንገድ ግንባታ፣ የአውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ የመሠረተ ልማት ዝርጋታ፣ የወጣቶች የሥራ ዕድል፣ የአካባቢውን ሀብት ለይቶ ማልማት እና በሌሎች ዘርፎች ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባን ብለዋል።

በቅድስት አባተ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast  YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version