Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በአፍሪካ ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ አንጎላን አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለት የመጀመሪያ ጨዋታ ደቡብ አፍሪካ አንጎላን 2 ለ 1 በማሸነፍ መርሐ ግብሩን በድል ጀምራለች፡፡
የደቡብ አፍሪካን የማሸነፊያ ግቦች ኦስዊን አፖሊስ እና ለይል ፎስተር ከመረብ ሲያሳርፉ፥ የአንጎላን ብቸኛ ግብ ደግሞ ሾው አስቆጥሯል።
ቀደም ሲል አመሻሽ 11:00 ሰዓት ላይ በተደረ ሌላኛው የምድብ ጨዋታ ማሊ እና ዛምቢያ 1 አቻ ተለያይተዋል።
በጨዋታው ላሲን ሲናዮኮ የማሊን ግብ ሲያስቆጥር ፓትሰን ዳካ የዛምቢያን ግብ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።
ዛሬ የሚካሄዱ የምድብ ጨዋታዎች ቀጥለው ሲያሆሄዱ ምሽት 5:00 ሰዓት ላይ ግብፅ ከዚምባብዌ ጋር ይገናኛሉ።
Exit mobile version