አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጣና በተለያዩ ዘርፎች ለሚሰማሩ ባለሃብቶች አስፈላጊው ድጋፍ ይደረጋል አለ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን።
በንግድ ቀጣናው ባለሃብቶች በሙሉ አቅማቸው ወደ ሥራ መግባት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍስሐ ይታገሱ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ የድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጣና የገቢና ወጪ ንግድን በማሳለጥ ረገድ ከፍተኛ ሚና አለው።
ነጻ የንግድ ቀጣናው በዓለም አቀፍ የንግድ እሴት ሰንሰለት ውስጥ የኢትዮጵያን ተሳትፎ በማሳደግ ዘመናዊ የነጻ ንግድ ቀጣና ሥርዓትን መዘርጋት ያስችላል ብለዋል።
እስካሁን 45 ባለሃብቶች በነጻ ንግድ ቀጣናው ለመሰማራት ውል መፈራረማቸውን አንስተው÷ ከእነዚህ ውስጥም 16ቱ ሥራ መጀመራቸውን ተናግረዋል።
በቀጣናው የተሰማሩ አልሚዎች በሙሉ አቅማቸው ወደ ሥራ እንዲገቡ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ነው የገለጹት።
በዚህ መሠረት በቀጣናው አስፈላጊ መሠረተ ልማቶች መሟላታቸውን ጠቅሰው÷ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥም የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመሩን አመልክተዋል።
በሌላ በኩል በነጻ የንግድ ቀጣናው የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጣና ለሚሰማሩ ባለሃብቶች አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።
ስለሆነም የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጣና መዋዕለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።
በመላኩ ገድፍ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook WMCC
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

