አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ የኢ-ኮሜርስ መተግበሪያና ሳጥን አልባ የመልዕክት አገልግሎት ይፋ አድርጓል፡፡
የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዳግማዊ አልዬ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም አገልግሎቱን የሚጠቀሙ ደንበኞችን አድራሻ በቀላሉ ማወቅ ያስችላል፡፡
ተቋሙ ላለፉት 132 ዓመታት መልዕክትን በታማኝነት ሲያደርስ መቆየቱን አውስተው፥ አሁን የኢትዮጵያ ፖስታ የዲጂታል ዘመን ላይ ደርሷል ብለዋል።
የቤት ለቤት አገልግሎትን ጨምሮ ደንበኞች በመረጡት አድራሻ መልዕክቶችን ያለ ምንም ተጨማሪ ክፍያ መቀበል ይችላሉ ነው ያሉት፡፡
ከየትኛዉም የውጪ ሀገር ያለምንም ችግር በቨርቹዋል ሳጥን አድራሻ መልዕክቶችን ማስላክ እንዲሁም የሚላኩ መልዕክቶችን የሞባይል ስልክን በመጠቀም መከታተል እንደሚቻል ጠቁመዋል፡፡
አዲሱ አገልግሎት በሀገር ውስጥ የሚላኩ ዶክመንቶች እንዲሁም አነስተኛ ጥቅል መልዕክቶችን መረጃ በየጊዜው በአጭር የጽሁፍ መልዕክት የሚያሳዉቅ መሆኑንም አስረድተዋል፡።
በሀይማኖት ወንድይራድ

