አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ16ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የሲዳማ ቡናን የማሸነፊያ ግቦች ብለስ ናጎ ፣ ዮሴፍ ዮሀንስና ፍራኦል መንግሥቱ አስቆጥረዋል።
በሌላ በኩል መቻል ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ ሁለቱንም የመቻልን ግቦች ፈቱዲን ጀማል ከመረብ አሳርፏል።
ቀደም ሲል በተደረገ የሊጉ ጨዋታ ኢትዮጵያ መድን እና ድሬዳዋ ከተማ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

