አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት የተለወጠ የሥራ ባህል፣ ነዋሪዎችን እና የልማት አጋሮችን በማስተባበር በሁሉም ዘርፎች የታቀዱ ሥራዎችን በአማካይ 95 ነጥብ 3 በመቶ ማሳካት ተችሏል አሉ።
የመዲናዋ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የመንግሥትና የፓርቲ ሥራዎች አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ባለፉት ስድስት ወራት በሁሉም ዘርፍ የታቀዱ ሥራዎችን በአማካይ 95 ነጥብ 3 በመቶ እንዲሳካ ላስቻሉ አመራሮች፣ ሰራተኞች እንዲሁም የልማት አጋሮችን ምስጋና አቅርበዋል።
የላቀ ውጤት ብናስመዘግብም በተቋማት ውስጥ ያሉ ክፍተቶችን በመለየት የትኩረት አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
መድረኩ ለቀጣዮቹ ስድስት ወራት ተጨማሪ አቅምና ተሞክሮ የምንሰንቅበት እንዲሁም የከተማችንን ነዋሪዎች በተሻለ ትጋትና ታማኝነት ለማገልገል የምንዘጋጅበት ይሆናል ሲሉም አመልክተዋል።

