አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር መቻል ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል።
ቀን 10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የመቻልን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ቸርነት ጉግሳ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተካሄደው የኢትዮ ኤሌክትሪክና ወላይታ ድቻ ጨዋታ ደግሞ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 ተጠናቅቋል።
ቀደም ብሎ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ምድረ ገነት ሽረ ያደረጉት ጨዋታ 0 ለ 0 መጠናቀቁ ይታወቃል፡፡

