Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

መቻል ኢትዮጵያ መድንን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር መቻል ኢትዮጵያ መድንን 1 ለ 0 አሸንፏል።

ቀን 10 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የመቻልን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ቸርነት ጉግሳ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተካሄደው የኢትዮ ኤሌክትሪክና ወላይታ ድቻ ጨዋታ ደግሞ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 ተጠናቅቋል።

ቀደም ብሎ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ምድረ ገነት ሽረ ያደረጉት ጨዋታ 0 ለ 0 መጠናቀቁ ይታወቃል፡፡

Exit mobile version