Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

7ኛው የመላ አፋር ስፖርት ውድድር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 7ኛው የመላ አፋር ስፖርት ውድድር “አንድነት ለጥንካሬያችን ስፖርት ለሠላማችን” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ነው፡፡

በም/ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ማህበራዊ ጉዳዮች አስተባባሪና የባህል፣ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ሐሚድ ዱላ እንዳሉት÷ ውድድሩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ስፖርተኞችን ማፍራት ያስችላል፡፡

በፈንቲ ረሱ እየተካሄደ የሚገኘው ውድድሩ ÷ መከባበር፣ መቻቻል እና አብሮነትን የሚያንጸባርቅ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጅራ በበኩላቸው ÷ ክልሉ ለስፖርቱ ዘርፍ ትኩረት በመስጠት ለመርሐ ግብሩ ያደረገው ዝግጅት የአመራሩን ጥንካሬ የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡

የለውጡ መንግሥት ለስፖርት ዘርፍ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል ያሉት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ መሐመድ አህመድ ዓሊ ናቸው፡፡

በኢትዮጵያ ብሎም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሊሆኑ የሚችሉ ስፖርተኞችን ለማፍራት ታቅዶ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝም አመልክተዋል፡፡

Exit mobile version