አዲስ አበባ፣ ጥር 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል እና ቼልሲ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል።
ሰንደርላንድን በኤምሬትስ ስታዲየም ያስተናገዱት አርሰናሎች 3 ለ 0 በማሸነፍ መሪነታቸውን አጠናክረዋል።
በጨዋታው የመድፈኞቹን ግቦች ማርቲን ዙቢሜንዲ እና ቪክቶር ዮኮሬሽ (2) ከመረብ አገናኝተዋል።
እንዲሁም በተመሳሳይ ሰዓት በተካሄደው የቼልሲ እና ዎልቭስ ጨዋታ ቼልሲ 3 ለ 1 ማሸነፍ ችሏል።
በጨዋታው የቼልሲን ሦስቱንም ግቦች ኮል ፓልመር (ሁለቱን በፍጹም ቅጣት ምት) ከመረብ ሲያሳርፍ የወልቭስን ብቸኛ ግብ ቶሉዋላሴ አሮኮዳሬ አስቆጥሯል።
በተመሳሳይ ሰዓት በተካሄዱ የሊጉ ጨዋታዎች አስቶንቪላ እና ቦርንማውዝን 1 ለ 1፣ ኤቨርተን ፉልሃምን 2 ለ 1፣ ዌስትሃም በርንሌይን 2 ለ 0 አሸንፈዋል።

