Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ቼልሲ በኖቲንግሃም ፎረስት ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ በኖቲንግሃም ፎረስት 3 ለ 1 ተሸንፏል።

አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በስታምፎርድ ብሪጅ በተደረገው ጨዋታ የኖቲንግሃም ፎረስትን የማሸነፊያ ግቦች አወንዬ (2) እና ኢጎር ጄሱስ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥረዋል፡፡

የቼልሲን ብቸኛ ግብ ደግሞ ብራዚላዊው ጃኦ ፔድሮ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በጨዋታው ቼልሲ ያገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ዕድል ኮል ፓልመር ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

Exit mobile version