አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ህክምና ትምህርት ክፍል በዛሬው ዕለት ካስመረቃቸው የ2018 ተመራቂ ተማሪዎች መካከል ዶ/ር ሙሉጌታ ደምስ አንዱ ነው።
ገና በልጅነቱ ሐኪም የመሆን ህልም እንደነበረው የተናገረው ዶ/ር ሙሉጌታ በዛሬው የምረቃ በዓል ላይ 3 ነጥብ 92 ውጤት በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።
ይህ ሽልማት የተለየ ስሜት እንደፈጠረለት የገለጸው ዶ/ር ሙሉጌታ፥ ዛሬ እኔ ሳልሆን ወላጆቼ ናቸው ያሸነፉት ብሏል።
ለዚህ ስኬቱ የበቃው በግል ጥረቱ፣ በጊዜ አጠቃቀሙ፣ በመምህራኑ ድጋፍና የወላጆቹ መስዋዕትነት መሆኑን ተናግሯል።
በሰለጠነበት የሕክምና ሙያ ሕዝቡን በታማኝነት ለማገልገል ዝግጁ መሆኑንም ነው የገለጸው።
በምናለ አየነው

