Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በሚደረጉ ውድድሮች ፍፃሜውን ያገኛል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በሚደረጉ ውድድሮች ይጠናቀቃል።

በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ላይ ኢትዮጵያን የወከሉ አትሌቶች የሚካፈሉባቸው 8 የፍፃሜ ውድድሮች ምሽት ላይ ይደረጋሉ።

በዚህም አመሻሽ 12:30 ላይ በከፍታ ዝላይ አትሌት ገመዶ አባተ እንዲሁም አመሻሽ 12:40 አትሌት ኦታጌ ኦባንግ በወንዶች የጦር ውርወራ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው ይወዳደራሉ።

ምሽት 1 ሰዓት ላይ ደግሞ በ3 ሺህ ሜትር የሴቶች መሰናክል ሩጫ ላይ አትሌት ወሰኔ አሰፋ እና አትሌት አልማዝ ዮሐንስ የሚሳተፉ ሲሆን÷ ምሽት 1:20 ላይ ደግሞ በ400 ሜትር የሴቶች መሰናክል አትሌት ደራርቱ እኖታ፣ አትሌት እመቤት ተከተል እና አትሌት ባንቻየሁ ተሰማ ኢትዮጵያን ይወክላሉ።

እንዲሁም ምሽት 1:50 ላይ የ1 ሺህ 500 ሜትር የሴቶች ሩጫ አትሌት አዳኑ ኔንቆ፣ አትሌት ማህተቤ ፍቃዱ እና አትሌት ደስታ ታደለ ተሳታፊ ናቸው።

ምሽት 2 ሰዓት ላይ የ1 ሺህ 500 ሜትር ወንዶች ሩጫ አትሌት እንዳሻው ረታና አትሌት አሸናፊ ኢማና ሲካፈሉት÷ ምሽት 2:20 ላይ ደግሞ በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ አትሌት ሙቢን ሀጂ፣ አትሌት ጀምበሩ ሲሳይ እና አትሌት ገብሩ አብረሃ ተፋላሚ ናቸው።

በመጨረሻም ምሽት 3 ሰዓት በ400 ሜትር የሴቶች ሩጫ አትሌት ገነት አየለ፣ አትሌት ምስጋና ኃይሉ፣ አትሌት ትዕግስት አያና እና አትሌት አጃይባ አልዪ ይወዳደራሉ።

በውድድሩ ኢትዮጵያ እስካሁን 11 ሜዳሊያዎች አስመዝግባለች።

በወርቅነህ ጋሻሁን

Exit mobile version