Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ ይገኛል፡፡

የክልሉ ምርጫ ጽሕፈት ቤት አስተባባሪ አቶ አብርሃም አንጁሎ እንደገለጹት÷ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በመጭው ሰኞ ለሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ሁሉን አቀፍ ዝግጅት ተደርጓል፡፡

በክልሉ የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተሰራጨ መሆኑን የገለጹት አስተባባሪው÷ የቁሳቁስ ስርጭቱ በጥንቃቄና ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ በጸጥታ ኃይል ታጅቦ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች እየተጓጓዘ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

የድምጽ መስጫ ወረቀትን ጨምሮ ሌሎች አስፈላጊ የምርጫ ቁሳቁስ ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በመሰራጨት ላይ መሆናቸውን ጠቅሰው÷ ጽሕፈት ቤቱ በተደራጀ መልኩ የቅደመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በክልሉ በሚገኙ 56 የምርጫ ክልሎች 3 ሺህ 941 የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውን አንስተው÷ በበሁሉም ምርጫ ጣቢያዎቹ የፊታችን ሰኞ ድምጽ እንደሚሰጥ አመልክተዋል።

ዜጎችም በምርጫው ዕለት የነቃ ተሰትፎ በማድረግ በወሰዱት ካርድ ድምጽ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በማስተዋል አሰፋ

Exit mobile version