አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን የጉመር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚውሉ የድምፅ መስጫ ቁሳቁስ ስርጭት ተከናውኗል፡፡
በጉመር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ሥር 46 የምርጫ ጣቢያዎች የሚገኙ ሲሆን ለእነዚህ ጣቢያዎች አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በተሽከርካሪዎች የማድረስ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።
የጉመር ቁጥር 1 ምርጫ ክልል ኃላፊ አቶ ሙባረክ ያሲን÷ የምርጫ ቁሳቁሶቹን በየምርጫ ጣቢያዎቹ የማድረሱንና ተደራሽ የማድረጉን ሥራ እስከ 7 ሰዓት ድረስ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያትመርጣለች #በምርጫብቻ #ፋናዲጂታል #Election #fanadigital #Ethiopia #Ethiopiavotes #Democracy #fanatelevision.

