የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት:-
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነጻነት ለማረጋገጥ፣ የረጅም ጊዜ የኢንዱስትሪ እድገትን እና ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካትን መሰረት ያደረጉ የተለያዩ የአምራች ዘርፉ እንቅስቃሴዎችን በንቃት መርተዋል፤ በዚህም የፋይናንስ አቅርቦትን ማሳደግ ላይ ያተኮረውን 4ኛውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በይፋ የከፈቱ ሲሆን፣ የወጣቶችን የስራ እድል ለማስፋፋትም በአዲስ ኣበባ የሚገኘውን የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መርቀው ከፍተዋል።
በተጨማሪም የታዳሽ ሃይል አቅምን ለማሳደግ አዲስ ስራ የጀመረውን የጎበዜ የሶላር ሴል ማምረቻ ፋብሪካን እንዲሁም፣ የአካባቢውን ጥሬ እቃዎች በመጠቀም የገቢ ምርቶችን ለመተካት ያለመውን በሞጆ ከተማ የሚገኘውን የግራንደር የሴራሚክ ማምረቻ ፋብሪካንም መርቀው ከፍተዋል።
የላቀ የጤና ስርዐትና ዘመናዊ አገልግሎቶች:-
ኢትዮጵያ በልዩና በላቀ የህክምና ብቃት ቀጣናዊ ማዕከል ለመሆን የምታደርገውን ስትራቴጂካዊ ጉዞ ግብ ለማሳካት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እጅግ በዘመኑ የህክምና ቴክኖሎጂዎች እና በሮቦቲክስ የታገዘውን እንዲሁም የካንሰር እና የልብና ህመሞችን በሀገር ውስጥ ለማከም የተገነባው ዘመናዊውን የላፍቶ ሆስፒታል በአዲስ አበባ በይፋ መርቀው ከፍተዋል፤ በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ የህክምና ስልጠና ላይ ለሚገኙ የሩዋንዳ እና ከሌሎች አፍሪካ ሀገራት ለመጡ የህክምና ባለሙያዎች ይፋዊ የእራት ግብዣ አድርገዋል።
መሰረተ ልማት፣ ዘላቂ አገልግሎቶች እና ትራንስፖርት:-
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የንግድና ማህበራዊ ትስስርን የሚጠናክረውንና የኢትዮጵያ አየር መንገድ 24ኛ የአገር ውስጥ መዳረሻ የሆነውን አዲሱን የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ መርቀዋል፤ በተጨማሪም በጎመሌ ወረዳ የሚገኘውን የደሴ ጎራ ግድብን ጨምሮ የፊና ኦሮሚያ መስኖ ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸውን የተከታተሉ ሲሆን ንጹህ ውሃ ለማቅረብና ለረጅም ጊዜ የሚዘልቅ የድርቅ መቋቋም አቅምን ለመገንባት የተነደፈውን መጠነ-ሰፊ የቦረና የውሃ አቅርቦት ፕሮጀክት ማስፋፊያ ስራ ጉብኝትንም በበላይነት መርተዋል።
የግብርና ትራንስፎርሜሽን እና የምግብ ሉዓላዊነት:-
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የክላስተር እርሻን ለማስፋፋት በዋና ዋና የግብርና ክልሎች የመስክ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በዚህም የሀገር ውስጥ የዩሪያ ማዳበሪያ ምርትን ለማሳደግ የታቀደውን የፋብሪካ ግንባታ ሂደት ለመገምገም ከአሊኮ ዳንጎቴ ጋር ወደ ጎዴ ተጉዘዋል። በተጨማሪም በምስራቅ ቦረና ዞን በሺዎች የሚቆጠሩ አባወራዎችና እማወራዎችን ያሳተፈውን መጠነ ሰፊ የክላስተር ግብርና ንቅናቄ የጎበኙ ሲሆን በሰሜን ሸዋ ዞን በብዙ ሄክታር መሬት ላይ የሚገኘውን የስንዴ እርሻ ልማትም ጎብኝተዋል።
የሚዲያ እና የብሔራዊ ፖሊሲ ሉዓላዊነት:-
የመንግሥት ተቋማትን እና የብሔራዊ ፖሊሲ ነጻነትን ለማጠናከር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሀገራዊ የምክክር መድረኮች ላይ ተገኝተዋል። ዲጂታላይዝድ ወደሆነ እና ራሱን ወደቻለ የስታቲስቲክስ ማዕቀፍ የሚደረገውን ሀገራዊ ሽግግር ለመደገፍ “የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ የተገኙ ሲሆን፤ በተጨማሪም የብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ወደ ትግበራ ምዕራፍ ሊሸጋገር የቀረበውን ይፋዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ተቀብለዋል። በዚሁ ወር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለብሔራዊ ልማት የሚረዱ የሚዲያ ስነ-ምግባር ሙያዊ መመሪያዎችን አስምረው የተናገሩበት እና “የሚዲያ እመርታ ለሀገር ግንባታ” በተሰኘው ብሔራዊ መድረክ ላይ ለሚዲያ ዘርፍ መሪዎች እና ባለሙያዎች ንግግር አድርገዋል።
የባህል ጥበቃ እና አከባቢያዊ እንክብካቤ:-
በኦሮሚያ ክልል የገዳ ሥርዓት ታሪክንና ፍልስፍናን ለመጠበቅ በያቤሎ ከተማ የተገነባውን የቦረና ባህል ማዕከል ጠቅላይ ሚኒስትሩ መርቀው የከፈቱ ሲሆን ማዕከሉ በመደመር መጽሐፍ ሽያጭ ገቢ የተደገፈ እንደሆነም ይታወሳል። ከዚህ ጎን ለጎን፣ የዱር እንስሳትና ብዝሃ-ሕይወት መጠበቂያ ሆኖ የሚያገለግለውን የቦረና ብሔራዊ ፓርክ መርቀው ከፍተዋል።
ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ እና የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን የሚያጠናክሩ ማዕቀፎች:-
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ አጋርነት ለማጠናከር በብሔራዊ ቤተ መንግሥት ከፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር የተወያዩ ሲሆን በብድር እና ተለያዩ ዘርፎች አጋርነት ላይ ስምምነቶችን አድርገዋል። በተጨማሪም በናይሮቢው አፍሪካ ፎርዋርድ ጉባኤ ላይ የተሳተፉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከተገበረቻቸው የልማት ሞዴሎች ልምድ ከማካፈላቸውም ባለፈ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክሪስታሊና ጆርጂየቫ ጋር የኢኮኖሚ ምክክር አድርገዋል።
በዚሁ ወር በጅቡቲ የፕሬዚዳንት እስማኤል ዑመር ጌሌን በዓለ-ሲመት የታደሙ ሲሆን ከኔዘርላንድስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮብ ዬተን ጋር የስልክ ውይይት አድርገዋል። በመጨረሻም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት 80ኛ ዓመት መታሰቢያ ምክንያት በማድረግ የቴምብር ስብስብ ይፋ አድርገዋል።

