Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የክልሉን የአርባ ምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው አገልግሎት አስጀመሩ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ በክልሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና አገልግሎት አሰጣጡን ለማሳደግ እየተሰራ ነው።

በዚህም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አካል የሆነውን የክልሉን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል በብቃት ማጠናቀቅ ተችሏል ብለዋል።

ማዕከሉ 4 የፌዴራል እና 6 የክልል ተቋማት አገልግሎትን በአንድ ጣሪያ ስር በማጣመር ከ15 በላይ አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት አመላክቷል።

Exit mobile version