አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ተማሪ የሆነው አንቲ ምትኩ 35 ‘A+’ በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳልያ ተሸልሟል፡፡
ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 679 ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
ከዩኒቨርሲቲው ተመራቂዎች መካከል የሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ ትምህርት ክፍል ተማሪ የሆነው አንቲ ምትኩ 3 ነጥብ 99 ውጤት የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ሆኗል።
ከ49 ኮርሶች 35 ‘A+’ እና 13 ‘A’ እንዲሁም 1 ‘A-‘ በማምጣት ነው የዩኒቨርሲቲው 8ኛ ዙር ምረቃ የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ የሆነው።
ተማሪ አንቲ ምትኩ በቀጣይም በተማረበት ሙያ ለሀገሩ የራሱን አሻራ ለማኖር እንደሚሰራ ተናግሯል፡፡
በዩሱፍ ጁሃር

