አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ቡና ገብረመድን ሀይሌን የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን አስታውቋል፡፡
አሰልጣኝ ገብረድህን ሀይሌ በሁለት ዓመት የኮንትራት ውል ነው የኢትዮጵያ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ለመሆን የተስማማው፡፡
ኢትዮጵያ ቡና ለቀድሞው ተጫዋች እና አንጋፋው አሰልጣኝ የእንኳን ደህና መጣህ መልዕክቱን ያስተላለፈ ሲሆን መልካም የአሰልጣኝነት ዘመን እንዲሆንለት ተመኝቷል፡፡

