Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የሀረሪ ክልል ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሀረሪ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት 10ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል፡፡

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ የ2018 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እያቀረቡ ሲሆን፥ ምክር ቤቱ በሪፖርቱ ላይ ከተወያየ በኋላ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡

በተጨማሪም የክልሉ ምክር ቤት ጽ/ቤት፣ የጠቅላይ ፍ/ቤት እና ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የ2018 ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እንደሚገመገም ነው የተገለጸው፡፡

የክልሉ መንግሥት የ2019 በጀት ዓመት እቅድ እና ረቂቅ በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቦ እንደሚጸድቅ ተመላክቷል፡፡

ምክር ቤቱ ለሁለት ቀናት በሚያካሂደው ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችንና ሹመቶችን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡

Exit mobile version