👉 ሀገራዊ ምክክሩ በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው፡፡
👉 በሀገራችን የነበሩትን ታሪካዊ ስብራቶች እንዲሁም የሐሳብ ልዩነቶች በጠብመንጃ እና በኃይል ሳይሆን በሰለጠነ መንገድ በምክክር ለመፍታት የሚያስችል አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ተከፍቷል፡፡
👉 ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው አሳታፊና አካታች በሆነ መልኩ ተካሂዷል፡፡
👉 ማንኛውም የህብረተስብ ክፍል ሳይገለል፤ የሁሉም ድምጽ እንዲሰማና እዲከበር በትኩረት ተሰርቷል፡፡
👉 በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ከአራቱም የሀገራችን ማዕዘናት 4 ሺህ ተመካካሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
👉 በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ለሀገራችን ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የሚያስችሉ በስምንት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ሰፊና ጥልቅ ምክከሮች ተካሂደዋል፡፡
👉 አጀንዳዎቹ የሀገራችንን መሰረታዊ ችግሮች የዳሰሱና ለነገዋ ኢትዮጵያ መሰረት የሚጥሉ ናቸው፡፡
👉 በመደማመጥና በመከባበር ለሀገራችን የተሻለ መፍትሄ በጋራ መፈለግ መቻላችን፤ ኢትዮጵያን አሁን ካለችበት ፈተና አውጥተው ወደተሻለ እና አዲስ ምዕራፍ የሚሻግሩ ናቸው፡፡
👉 ይህ የጀመርነው የመደማማጥ ባህል ደምቆ ለትውልድ እንዲሻገር፤ ዘላቂ እሴታችን ይሆን ዘንድ የሁላችንም ቁርጠኝነት ያሰፈልጋል፡፡
በትዕግስት ግዛቸው
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ በሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የመዝጊያ ሥነ ሥርዓት ላይ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

