👉 ምክክሩ ፖለቲካዊ ተቃርኖ በይቅርታና በምክክር ጎዳና እንዲተካ መሰረት ጥሏል፡፡
👉 ውጤቱ ለአሁኑ ብቻ ሳይሆን ለመጪው ትውልድ የሚተላለፍ አሻራ ነው፡፡
👉 የሀገር ብርታት ያለው ልዩነትን በሰለጠነ መንገድ በውይይት መፍታት ላይ ነው፡፡
👉 የዛሬዋ እለት ድምቀቷ እና ቁም ነገሯ ለሀገር የሚበጅ ለትውልድ የሚዋጅ አንድነታችንን የሚያጸና መልካም ተስፋችንን የሚያለመልም ሁኔታን የሰማንባት መሆንዋ ነው፡፡
👉 የ130 ሚሊየን ህዝብን ሀሳብ ተሸክሞ ኃላፊነት ውሰድ ቀላል አይደለም፡፡
👉 ተመካካሪዎች የነገን የህብር አንድነት እንድናይ፣ የሀሳብ የበላይነት እንዲሰፍን ማድረጋችሁ ታሪካዊ ስኬት ነው፡፡
👉 በምክክሩ ለነገው ትውልድ የሚሻገር አሻራ ተቀምጧል፡፡
👉 በሀገራዊ ምክክር የቀረቡ ሃሳቦች ለፖለቲካዊ ልምምዳችን እና ለሀገር ግንባታ ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው፡፡
👉 ምክክሩ የሁላችንም የሆነችውን ኢትዮጵያ የሚገልጹና የሚያጹኑ የጋራ ርዕይ እና እጣ ፈንታ በአንድ ላይ ለማስኬድ የሚያስችል እውቀት የተጨበጠበት ነው፡፡
👉 የምክክሩ ማህበራዊ ፋይዳ በመከባበር እና በሰመረ ቋንቋ ከኃለ ቃል በጸዳ መልኩ ለመወያየት የሚያስችል አቅም እንዳለን አሳይቷል፡፡
👉 በማህበራዊ አውዳችን ውስጥ መልክ መያዝ የሚኖርባቸዉ የፖለቲካ ቃላት እና ስንኞች ሰከን ያሉ እንዲሆኑ ተጨባጭ ልምድ ሰጥቷል፡፡
በእመቤት ሲሳይ
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የመዝጊያ ሥነ ሥርዓት ላይ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-

