አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በርንማውዝን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
በአዲስ አሰልጣኝ የተመራው ማንቼስተር ሲቲ በርንማውዝን በማሸነፍ በሊጉ መርሐ ግብር የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል፡፡
ማርከስ ታቨርኔር በርንማውዝን በ26ኛው ደቂቃ ቀዳሚ ያደረገ ቢሆንም ማርክ ጉሂ በ85 እና ገቫረዲዮል በ92 ደቂቃ ባስቆጠሯቸው ግቦች ሲቲ ጨዋታውን 2 ለ 1 ማሸነፍ ችሏል፡፡
በሌላ በኩል የአምናው የአውሮፓ ሊግ አሸናፊ አስቶን ቪላ በብራይተን የ4 ለ 0 ሽንፈትን አስተናግዷል፡፡

