Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በሳዑዲ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 2 ሺህ 463 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 2 ሺህ 463 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

ተመላሾቹ 2 ሺህ 462 ወንዶች እና 1 ሴት ሲሆኑ ÷ ከእነዚህ መካከልም 57 ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኛሉ።

መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም በተጀመረው ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ሥራ እስካሁን ከ98 ሺህ 900 በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

ለተመላሽ ዜጎች በአውሮፕላን ማረፊያ እና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ተገልጿል፡፡

Exit mobile version