አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) አቶ ኢሳያስ ጂራ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆነው ተመርጠዋል።
ብቸኛ ተወዳዳሪ ሆነው የቀረቡት እና ላለፉት 8 ዓመታት የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ሆነው የመሩት አቶ ኢሳያስ ጂራ ከተሰጡ 88 ድምጾች 81 ድምጽ በማግኘት ለ3ኛ ጊዜ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት በመሆን መመረጥ ችለዋል፡፡
አቶ ኢሳያስ ጂራ ለቀጣዮቹ አራት ዓመታት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆነው የሚቀጥሉ ይሆናል፡፡

