Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለሶስት ምሁራን የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጠ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 4፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቦርድ በትናትናው ዕለት ለሶስት ምሁራን የፕሮፌሰርነት ማዕረግ መስጠቱን አስታወቀ።
በዚህም ዩኒቨርሲቲው ለዶክተር ታደሰ አወቀ ፣ ለዶክተር የማታው ወንዴ እና ለዶክተር አሰግድ ደምሴ ሙሉ የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።
ዩኒቨርሲቲው በፌስቡክ ገፁ ባወጣው ፅሁፍ የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ለተሰጣቸው ምሁራን የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፏል።
Exit mobile version