Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ሀገራዊ የስጋት ተጋላጭነት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 4 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሁለተኛው ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመደገፍ እንዲሁም ተያያዥ የፋይናንስና የኢኮኖሚ ወንጀሎች ጥናት በይፋ ተከፍቷል።
የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ዝግጅቱን በይፋ ሲከፍቱ÷ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ስርዓት ለመግባት እየተዘጋጀች ባለችበት ወቅት የዓለም ባንክ እያበረከተ ላለው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።
የዓለም ባንክ ግሩፕ የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ኦስማን ዲዮን በበኩላቸው÷ ኢትዮጵያ የገንዘብ ወንጀልን በብቃት ለመቋቋም የሚያስችል ጠንካራ ስርዓት ለመዘርጋት በምታደርገው ጥረት ተቋማቸው አጋር ሆኖ እንደሚቀጥል መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
#FBC
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።
Exit mobile version