አዲስ አበባ ፣ህዳር 3 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሱዳን ዳርፉር የተሰማራው 24ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ ግዳጁን አጠናቆ ለተተኪው 25ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስከባሪ ሻለቃ አስረከበ ።
በወቅቱም የአስረካቢው ሻለቃ አዛዥ ኮሎኔል አድማሱ ተክሌ ÷ ምንም እንኳን የግዳጁ ባህሪ ውስብስብና አስቸጋሪ ቢሆንም ሻለቃው አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ ችሏል ብለዋል ፡፡
የተረካቢው ሻለቃ አዛዥ ኮሎኔል ተፈራ መላክ በበኩላቸው ÷ ከአስረካቢው ሻለቃ ያገኘናቸውን ተሞክሮዎች እንደ ግብአት በመጠቀምና ጠንክረን በመስራት ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ ያላትን ተፈላጊነትና መልካም ስም እናስጠብቃለን ማለታቸውን ከኢፌዲሪ የመከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ፡፡
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።

