Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በኢሉ አባቦር ዞን 12 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 21 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢሉ አባቦር ዞን 12 የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢሉ አባቦር ዞን ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡

በተጨማሪም 34 የጦር መሳሪያዎችና በርካታ ጥይቶች መያዛቸውንም አስታውቋል፡፡

የዞኑ ፖሊስ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ኮማንደር ዓለሙ ታደሰ እንደገለጹት፥ በዞኑ የጸጥታ አካላት በቅንጅት ባደረጉት ፍተሻ 645 ሺህ ብር ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች፣ እንዲሁም 16 ሺህ 800 ሐሰተኛ የብር ኖቶች መያዛቸውን ኦ ቢ ኤን ዘግቧል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version