Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የጠ/ሚ አብይ አህመድን መልዕክት ተቀበሉ

አዲስ አበባ ፣ ጥር 19፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኬንያ ፕሬዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ከኢፌዴሪ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ይ አህመድ የተላከ መልዕክት ዛሬ በቤተመንግስታቸው ተቀበሉ።

መልዕክቱን ለፕሬዚዳንት ኡሁሩ ያደረሱት የኤፌዴሪ የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር እና የዶክተር አብይ ልዩ መልዕክተኛ አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ ናቸው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የሚገኙበት ልዑክ ከኬንያ መንግስት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ውይይት አድርገዋል።

አቶ ኃ/ማርያም እና ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ያደረጉት ውይይት በሁለትዮሽ፥ በአካባቢያዊ የሰላምና ፀጥታ ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ ነበር።

የኬንያው ፕሬዚዳንት ሁለቱ አገሮች ለአካባቢው ሰላም ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።

የኢትዮ-ኬንያ ወዳጅነት እኛ የፈጠርነው ሳይሆን በትውልዶች ሽግግር እየጎለበተ የመጣ በመሆኑ የበለጠ ልናጠናክረው ይገባል ብለዋል።

በአቶ ኃ/ማርያም የተመራው ልዑክ በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲን በመጎብጀት ከዲፕሎማቶች ጋር መወያየታቸውን ከኤምባሲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version