Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የአማራ ክልል ምክር ቤት የክልሉን ሰንደቅ ዓላማ ለመቀየር የቀረበውን አዋጅ አፀደቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የአማራ ክልል ምክር ቤት የክልሉን ሰንደቅ ዓላማ ለመቀየር የቀረበውን አዋጅ አፅድቋል።

በቀጣይ 6 ወራት በጥናት ላይ ተመስርቶ የአማራ ህዝብን ታሪክና ስነ ልቦና የሚያንፀባርቅ ሰንደቅ ዓላማ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ እንዲውልም ምክር ቤቱ ውሳኔ አስተላልፏል።

ነባሩ ሰንደቅ ዓላማ አንድን ፓርቲ የሚወክል እንጂ የአማራ ህዝብን ስነ ልቦና የማያንፀባርቅ በመሆኑ በህዝቡ ተቀባይነት ማጣቱም በምክር ቤቱ ተገልጿል።

እንደ ኢብኮ ዘገባ ምክር ቤቱ 3ኛ ቀኑን በያዘው 17ኛ መደበኛ ጉባኤው የቴምብር ቀረጥ ማሻሻያ አዋጅንና የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅን ገምግሞ አፅድቋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version