Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የንግድ ስምምነት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ የዓሳ ምርት ከሞቃዲሾ  ወደ አዲስ አበባ መላክ የሚያስችል  የንግድ ስምምነት ተፈራርመዋል ፡፡

ስምምነቱን የተፈራረሙት በሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር አብዱልፈታህ አብዱላሂ ሀሰን እና የሶማሊያ የአሳ ሀብት  ልማት ሚኒስቴር አብዲዛዝ ሀጅ በሽር መሆናቸውን ከሶማሊያ ስታር ፖስት ጋዜጣ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ኢትዮጵያ ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ ሁለገብ ትብብር ለማድረግ የሶስትዮሽ ስምምነት መፈራረማቸው የሚታወስ ነው ፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version