Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የአሜሪካ ጦር በአፍጋኒስታን የነበረውን ጦር ሰፈር ለቆ መውጣቱ ተሰማ

BAGRAM AIR BASE, AFGHANISTAN - MAY 11: U.S. Army soldiers walk to their C-17 cargo plane for departure May 11, 2013 at Bagram Air Base, Afghanistan. U.S. soldiers and marines are part of the NATO troop withdrawal from Afghanistan, to be completed by the end of 2014. (Photo by Robert Nickelsberg/Getty Images)

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍጋኒስታን የሚገኘው የአሜሪካ ጦር ባግራም የተሰኘውን የጦር ሰፈር ለቆ መውጣቱ ተገልጿል፡፡

ወታደሮቹ ስፍራውን ለቀው የወጡት ዋሽንግተን ከታሊባን ጋር በገባችው ስምምነት መሰረት መሆኑን የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለስልጣናት ተናግረዋል፡፡

ይህን ተከትሎም ለ20 ዓመታት በአፍጋኒስታን ሰላም በማስከበር ሂደት ላይ የቆዩት የአሜሪካ እና የሰሜን ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ወታደሮች ባግራም የተሰኘውን የጦር ሰፈር በዛሬው ዕለት ለቀው መውጣታቸው ተገልጿል፡፡

ወታደሮቹ የጦር ሰፈሩን ለቀው መውታጣቸውም አሜሪካ በአፍጋኒስታን የነበራት ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት ማብቃቱን ያረጋግጣል ነው የተባለው፡፡

አሁን ላይም የጦር ሰፈሩ በአፍጋኒስታን መንግስት ወታደሮች ቁጥጥር ስር መሆኑ ነው የተገለጸው፡፡

በጦር ሰፈሩ ከ2 ሺህ 500 እስከ 3 ሺህ 500 የሚደርሱ የአሜሪካ ሰላም አስከባሪ ወታደሮች ይኖሩ ነበር፡፡

ምንጭ፦ ሬውተርስ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን፡፡

Exit mobile version